የኮሌጃችን አመራሮች ከመምህራን እና አስተዳደር ሰራተኞች ጋር የ2017 በጀት አመት የ6 ወር የስራ አፈጻጸም ግምገማ እና ውይይት በዛሬው እለት አካሂደዋል።
በዚህ ፕሮግራም በኮሌጁ የሚገኙ ሁሉም የስራ ቡድኖች እና የስራ ክፍሎች የ6ወር የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን በሁሉም የስራ ክፍሎች ታቅደው በተከናወኑ ዝርዝር ተግባራት፣ ያጋጠሙ ችግሮች፣ የተወሰዱ መፍትሄዎች እና ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች እንዲሁም የኮሌጁን የ2015 እና የ2016 አጠቃላይ የኦዲት ሪፖርት የቀረበ ሲሆን በቀረቡት ሪፖርቶች ላይ ጥያቄ ፣ ሀሳብ፣አስተያየት ተሰጥቶበታል።
ለቀረቡት ጥያቄና ሀሳቦችም ሪፖርት አቅራቢዎች ምላሽ በመስጠት እና የኮሌጁ ዲን አቶ በዛብህ ይመር ከኮሌጁ ሰራተኞች ጋር አጠቃላይ ዉይይቶችን በማድረግ የማጠቃለያ ሀሳብ እና ምላሾችን በመስጠት ፕሮግራሙን አጠናቋል።
ኮምቦልቻ ግብርና ኮሌጅ ህዝብ ግንኙነት
ኮ/ግ/ኮ 26/5/2017 ዓ/ም