የፅህፈት መሳሪያና የት/ቤት ግብዓት ድጋፍ ተደረገ

መስከረም 13/2015 ዓ.ም
ኮምቦልቻ ግብርና ኮሌጅ ህ/ግንኙነት
ድጋፉ የተደረገው አዲሱን አመት ምክንያት በማድረግ ለቃሉ ወረዳ ቀበሌ 034 ለሚገኙና በቀበሌ አስተዳደሩ ለተለዩ የዘማች ልጆችና በዝቅተኛ ኑሮ ደረጃ ለሚገኙ 100 ለሚሆኑየአንደኛና የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች ነው፡፡
ከድጋፉ ጎን በጎን በቦታው የተገኙት የኮሌጁ ዲን፣ አካ/ምክትል ዲን፣ አስ/ልማት ም/ዲን እና መምህር ዘመነ ሹምየ ለህፃናቱ ትምህርት የችግሮች ሁሉ መፍቻ ቀልፍ መሆኑን ጠቁመው የተሻለ ደረጃ ለመድረስ በትጋት እንዲማሩ ምክር አዘል መልእክት አስተላልፈዋል፡፡
ድጋፉን የተረከቡት የቀበሌው አስታዳዳሪ አቶ ኡመር ታደሠ በኩላቸው ግብርና ኮሌጁ ላለፉት ዓመታትም ከጎናቸው እንደነበረና በርካታ ድጋፍ ማድረጉን አስታውስው ለዚህም ተግባሩ የላቀ ምስጋና ይገበዋል ሲሉ ገልፀዋል፡፡
በተጨማሪም ለቀበሌው ት/ቤት የሚውል የጥቁር ሰሌዳ፣ የወንበርና ጠረንጴዛ እንዲሁም የደስክቶፕ ኮ ምፒውተር በኮሌጁ ማኔጅመንት ውሳኔ መሠረት ድጋፍ መደረጉንም የኮሌጁ ዲን በንግግራቸው አሳውቀዋል፡፡
በጥቅሉ በዛሬው እለት ዲጋፍ የተደረጉ ቁሳቁሶች ግምታቸው ከ300 ሽህ ብር በላይ መሆኑን የኮሌጁ አስ/ል/ምክትል ዲን አቶ ዛብህ ይመር በንግግራቸው አሳውቀዋል፡፡
የኮሌጁ አመራርሮችና የስራ ባልደረቦች በመጨረሻም በኮሌጁ የሰርቶ ማሳያ እርሻ ላይ የለሙ የጤፍና የስንዴ
ሰብሎችን ጎብኝተው ተመልሰዋል፡፡
Share on facebook
Share on linkedin
Share on twitter
Share on email

Related

Notices

  • Announcements
  • Vacancy
  • Call For Papers
  • Bids

Downloads

  • Registrar
  • Budget and Finance
  • Policies and Legislations
  • Research and Technology Transfer

Partenerships

  • ARSBA
    Amhara National Regional State Bureau of Agriculture
  • Ministry of Labor and Skills
    Ministry of Labor and Skill
  • wollo unversity
    Wollo Unversity
  • SNV
    SNV Ethiopia
  • giz
    GIZ Ethiopia
  • Smis
    Small and Micro Irrigation Support
Archives